ከሊቀመንበሩ ማኅደር university conducted 11th annual

12
1 MIDROC Newsletter Volume 13, Issue # 67 April — June 2012 Addis Ababa, Ethiopia Queens Supermarket Launches new branch Queens Supermarket, a member of MIDROC Ethiopia Technology Group, inaugurated its 7 th modern branch at Mechare Corporate Center on 13 July 2012. Speaking at the inaugural ceremony, MIDROC Ethiopia CEO, Dr. Arega Yirdaw applaud Sheik Mohammed Husein Ali Al-Amoudi for his የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ አባል የሆነው ኩዊንስ ሱፐርማርኬት ኃ.የተ.የግል.ማህበር የቴክሎጂ ግሩፕ ኮርፖሬት ማዕከል በሆነው መቻሬ ሜዳ ግቢ ውስጥ ዘመናዊ ቅርንጫፍ ሱፐርማርኬት ሐምሌ 5 ቀን 2004 ዓ.ም በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቀ፡፡ ዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቺፍ ኢግዚኪዩቲቭ ኦፊሰር የምረቃ ሥነ-ሥርአቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የቴክኖሎጂ ግሩፑ ኩባንያዎች ሥራቸውን የማስፋፋት ኩዊንስ ሱፐርማርኬት ቅርንጫፍ የመሸጫ ቦታ ከፈተ ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11 th Annual Multidisciplinary research Conference ሱፐርማርኬቱ ተመርቆ ሲከፈት «ድህነትን ለማጥፋት በርትታችሁ ሥሩ። ... ለሀገራችሁ በመሥራት የልማት አጋርነታችሁን ልታሳዩ ይገባል» *** «ሀገራችን በተያያዘችው የልማት ጐዳና የግድብ የመንገድ የባቡር ሀዲድ ዝርጋታና ሌሎች ሥራዎች ፈጣሪ ተጨምሮበት የተሻለ ደረጃ እንዲደርስና ስኬታማ እንዲሆኑ እመኛለሁ።» ሊቀመንበራችን ሼህ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ መስከረም 28 ቀን 2004 ዓ.ም. በዘጠነኛው የደምበኞች የሠራተኞና የቤተሰብ በዓል ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ በመተሃራ ............................ገፅ 2 ...............................................Page 3 UU Conducted Effective Communication training......Page 5 የኮስፒ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት....................ገፅ 6 ለሴት ሠራተኞች በካንሠር ላይ ትምህርት ተሰጠ...................ገፅ 7 የዜግነት ኃላፊነት ለመወጣት .......................................ገፅ 8 ገፀ ብዙው የአመራር ጠቢብ .........................................ገፅ 9 ጠቅላላ ዕውቀት...........................................................ገፅ 11 መልዕክት ከሲ.ኢ.ኦ......................................................ገፅ 12 Volume 13, Issue No. 67 April — June 2012 From Chairman’s File u¨<eØ Ñ뉋” Continued on page 4 See full text on page 5 Inside Pages ወደ ገጽ 4 ዞሯል 4 4 4 4 4 4 4 4 4 Participants while attending the conference

Upload: nguyennhi

Post on 03-Jan-2017

247 views

Category:

Documents


3 download

TRANSCRIPT

Page 1: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

1

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

Queens Supermarket Launches new branch

Queens Supermarket, a

member of MIDROC Ethiopia

Technology Group, inaugurated

its 7th modern branch at

Mechare Corporate Center on

13 July 2012.

Speaking at the inaugural

ceremony, MIDROC Ethiopia

CEO, Dr. Arega Yirdaw

applaud Sheik Mohammed

Husein Ali Al-Amoudi for his

የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ አባል የሆነው ኩዊንስ ሱፐርማርኬት ኃ.የተ.የግል.ማህበር የቴክሎጂ ግሩፕ ኮርፖሬት ማዕከል በሆነው መቻሬ ሜዳ ግቢ ውስጥ ዘመናዊ ቅርንጫፍ ሱፐርማርኬት ሐምሌ 5 ቀን 2004 ዓ.ም በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቀ፡፡

ዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቺፍ ኢግዚኪዩቲቭ ኦፊሰር የምረቃ ሥነ-ሥርአቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የቴክኖሎጂ ግሩፑ ኩባንያዎች ሥራቸውን የማስፋፋት

ኩዊንስ ሱፐርማርኬት ቅርንጫፍ የመሸጫ ቦታ ከፈተ

ከሊቀመንበሩ ማኅደር

University Conducted 11th Annual Multidisciplinary research Conference

ሱፐርማርኬቱ ተመርቆ ሲከፈት

«ድህነትን ለማጥፋት በርትታችሁ ሥሩ። ... ለሀገራችሁ በመሥራት የልማት አጋርነታችሁን

ልታሳዩ ይገባል»

***

«ሀገራችን በተያያዘችው የልማት ጐዳና የግድብ የመንገድ የባቡር ሀዲድ ዝርጋታና ሌሎች ሥራዎች ፈጣሪ ተጨምሮበት የተሻለ ደረጃ እንዲደርስና ስኬታማ እንዲሆኑ እመኛለሁ።»

ሊቀመንበራችን ሼህ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ መስከረም 28 ቀን 2004 ዓ.ም. በዘጠነኛው የደምበኞች

የሠራተኞና የቤተሰብ በዓል ላይ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ

ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ በመተሃራ ............................ገፅ 2 ...............................................Page 3

UU Conducted Effective Communication training......Page 5የኮስፒ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት....................ገፅ 6ለሴት ሠራተኞች በካንሠር ላይ ትምህርት ተሰጠ...................ገፅ 7

የዜግነት ኃላፊነት ለመወጣት .......................................ገፅ 8ገፀ ብዙው የአመራር ጠቢብ .........................................ገፅ 9ጠቅላላ ዕውቀት...........................................................ገፅ 11መልዕክት ከሲ.ኢ.ኦ......................................................ገፅ 12

Volume 13, Issue No. 67 April — June 2012

From Chairman’s File

u¨<eØ Ñ뉋”

Continued on page 4

See full text on page 5

Inside Pages

ወደ ገጽ 4 ዞሯል

4444

4

4

4

4

4

Participants while attending the conference

Page 2: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

2

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ በመተሃራ ዘመናዊ የኤክስፖርት ቄራ አስመረቀ

የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኩባንያዎች አባል የሆነው ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግል ማኅበር በመተሃራ ዘመናዊ የኤክስፖርት ቄራ የማሻሻያ ግንባታ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በተሳካ ሁኔታ ገንብቶ ሚያዝያ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. አስመረቀ።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ወንድይራድ ማንደፍሮ ባደረጉት ንግግር መንግሥት በአግሮ ኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሚካሄዱ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ድጋፍ እንደሚያደርግ አብራርተዋል።

ዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ኦፊሰር ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፣ ኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ስድስት ቄራዎች እንዳሉት ጠቁመው የመተሀራ የኤክስፖርት ቄራ ዓለም አቀፍ ደረጃን ባሟላ ሁኔታ የማሻሻያ ግንባታ በማካሄዱ ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ከማስገኘት ባሻገር ለአካባቢው አርብቶ አደር ትልቅ የገቢ ምንጭ እንደሚፈጥር አስረድተዋል።

ሼክ አብደላ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ በበኩላቸው በድርጅታቸው አማካኝነት ኤልፎራ ወደ ውጭ የሚልከው የሥጋ ምርት በአረብ አገራት ተመራጭ እንዲሆን የሚያስችሉ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ቃል ገብተዋል።

አቶ ዘለቀ መንግሥቴ የኤልፎራ አግሮ ኢንዱስትሪ ዋና ሥራ አስኪያጅ ስለ መተሃራ ቄራ የማሻሻያ ፕሮጀክት ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት ኩባንያው ትኩስ የእንስሳት ሥጋን ከነአጥንቱ (ካርካስ) በጥራት ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ እንዲያስችለው ያስገነባው የእርድ ማከናወኛ ቦታ በዘመናዊ የማረጃ ማሽን የተደራጀ እና በአንድ ጊዜ 18 ቶን የበግና የፍየል እርድ በማከናወን በማቀዝቀዣ ቦታ በማቆየት ለሽያጭ ማቅረብ የሚችል ነው፡፡

የመተሃራ ቄራ በሣምንት ሦስት ቀን በሚያከናውነው እርድ 54 ቶን፤ በወር 216 ቶን፤ በ11 ወራት ደግሞ 2,400 ቶን ሥጋ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችለው ዘመናዊ ቄራ ሲሆን፤ ለሥጋው ጥራት የሚያስፈልገው የሙቀት መቆጣጠሪያ መሣሪያም በሚገባ የተገጠመለት ነው፡፡ ይህም አሁን ባለው የኤክስፖርት ዋጋ ሲሰላ በዓመት 12 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያህል ገቢ እንደሚያገኝ ይገመታል፡፡

ቄራው የዓመቱን የሥጋ አቅርቦት ለማሟላት የሚያስፈልገው የቁም እንስሳት ብዛት (በግና ፍየል) 360,000 ያህል በመሆኑ ለአካባቢው አርብቶ አደር ህብረተሰብ ሰፊ የገበያ ዕድል እንደሚፈጥር ይታመናል።

ቄራው በቁም እንስሳት ማቆያ በረቶቹ 10,000 አነስተኛ እንስሳትና 4,000 የዳልጋ ከብቶች የመያዝ አቅም አለው፡፡ በዕርድ ወቅት የተረፈ ምርት ማስወገጃ እንዲሁም ምርቱን ወደ ውጭ ለመላክ ወደ አየር መንገድ መውሰጃ ማቀዝቀዣ በተገጠመላቸው ዘመናዊ መኪናዎች የተደራጀ ነው፡፡

የመተሃራ ቄራ እ.ኤ.አ በ2007 ዓ.ም ከግል ባለሀብት የተገዛ ሲሆን፣ እ.ኤ.አ ከግንቦት ወር 2008 ዓ.ም በግብርና ሚኒስቴር እና ከተባበሩት አረብ ኤምሬት የመጡ የመስኩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎች እንዲሁም የግብርና ሚኒስቴር የእንስሳት እፅዋት ጤና እና ቁጥጥር ጥራት ባለሙያዎች በተከታታይ የሰጡትን ሙያዊ የማሻሻያ ሀሳቦችን በመቀበል ሥራው በ2010 ተጀምሯል፡፡

የቄራ ማሻሻሉ ሥራ በኤልፎራ ባለሙያዎች እና በአብደላ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ ኢስታብልሽንመንት በተባለ የውጭ ድርጅት ጥምረት የተከናወነ ሲሆን፤ሳማራ ትሬዲንግ ኢስታብልሽመንት የተባለ የውጪ ድርጅትም በተባባሪነት ተሳትፏል፡፡

በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የፌዴራል መንግሥት ባለሥልጣናት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የምሥራቅ ሸዋ ዞን አስተዳደር፣ የመተሃራ ከተማ መስተዳድር ጽ/ቤት፣ የፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር ጽ/ቤት እና የአካባቢው ታዋቂ ሰዎች እንዲሁም የሀገርና የውጭ ገበያ ድርጅቶችና ባለሙያዎች፣ የኤልፎራ የገበያ ማዕከል ደንበኞች እና የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኩባንያዎች የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ELFORA Inaugurated Metehara export abattoir

ELFORA Agro Industry P.L.C., a member of the MIDROC Ethiopia Technology Group Companies, Inaugurated modern abattoir at Metehara town in the presence of Agriculture State Minister Wondyirad Mandefro, Senior Government officials, Sheik Abdulla Hussien Al-Amoudi, company managers and other dignitaries on April 29, 2012.

Inaugurating the abattoir, State Minister H.E. Ato Wondyirad Mandefro said government would offer incentive for investors engaged in value added agriculture products destined for export markets.

Government is working closely with stakeholders to make the livestock value chain system more effective, State Minister further stated that and efficient up to the destination markets. He added government has designed a supportive package for investors engaged in meat processing in Somali State which has immense sheep and goat resources.

The MIDROC Ethiopia Chief Executive Officer, Dr. Arega Yirdaw on his part said the abattoir, located at an ideal place for meat processing business, would help boost the export trade in the sector.

He said the abattoirs at Metehara and Bishoftu have got international recognition.

ELFORA Agro Industry PLC Manager Zeleke Mengiste explained that the abattoir can supply 18 tons of sheep and goat meat at a time for the market and is expected to generate 12 million US dollars a year.

ቄራው በተመረቀበት ወቅት

የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ስጦታ ሲሰጥ

Page 3: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

3

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

Page 4: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

4

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

Queens Supermarket ...ኩዊንስ ሱፐርማርኬት...

ሂደታቸው እንዲጠናከር፣ የሥራ ዕድል እንዲሠፋና ጥራቱ የተጠበቀና አስተማማኝ ምርት በማቅረብ ደንበኞቻችንን እንድናረካ ሊቀመንበር ሼክ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ ለሚያደርጉልን ያልተቋጠ ድጋፍ በቅድሚያ ምሥጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል። በዋናነት ሠራተኛውና መላው ማኔጅመንት ለኩዊንስ ቅርንጫፍ መከፈት ላደረገው አስተዋጽኦ ሊመሰገን እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

ሲኢኦ አያይዘውም፣ የኩዊንስ ሱፐርማርኬት ከሾላ ቅርንጫፍ ቀጥሎ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገባው በሜክሲኮ በሚገኘው ቅርንጫፍ እንደነበር ጠቁመው በልማት ምክንያት ከቦታው በመነሳታችንና ሥራው በመቆሙ በመቻሬ ሜዳ አዲስ ቅርንጫፍ መከፈቱ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የመቻሬ ኩዊንስ ቅርንጫፍ ለደንበኞች መስተንግዶ አመቺነት ያለውና የቴክኖሎጂ ግሩፑ ሠራተኞች ሊገለገሉበት የሚችሉበት መሆኑንም አስረድተዋል። በቀጣይም ኩባንያው ከሱፐርማርኬት ሥራ በተጓዳኝ በልዩ ልዩ የአገልግሎት ዘርፍ ደንበኞቹን ለማርካት እንደሚሠራ ጠቁመዋል፡፡

ወ/ሮ ታህሳስ ወንድምነህ የኩዊንስ ሱፐርማርኬት ዋና ሥራ አስኪያጅ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር ኩባንያው ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ እንዲስፋፋና እንዲጠናከር በተለይ ሲኢኦ ለሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ምሥጋና አቅርበዋል፡፡

ወ/ሮ ታህሳስ አያይዘውም የሲኢኦ ቢሮ፣ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቹ የሥራ ኃላፊዎች እና የኩባንያው ሠራተኞች አስተዋጽኦም የላቀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጅዋ እንዳሉት በተለይ የሜክሲኮ ቅርንጫፍ ሱፐርማርኬት በልማት መነሳት ሳቢያ ሥራው በመቋረጡ በኩባንያው ገቢ ላይ ተጽዕኖ አሳድሮ እንደነበር ጠቁመው፣ ሲኢኦ ባስተላለፉት ውሳኔ መሠረት በ3 ሚሊዮን ብር ኢንቨስትመንት አዲስ ቅርንጫፍ ለመክፈት መብቃቱን አስረድተዋል፡፡ በዚህም ለ15 ቋሚ ሠራተኞች የሥራ ዕድል መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡

በመቻሬ ቅርንጫፍ ከሱፐርማርኬት አገልግሎት በተጨማሪ የካፊቴሪያ እና የመሳሰሉት አገልግሎት የማስፋፋት ዕቅድ መኖሩን ወ/ሮ ታህሳስ ጠቁመዋል።

ቅርንጫፉ የምርት ማዘጋጃ፣ ማሸጊያና ማከማቻ የሚሆን ዘመናዊ መሣሪያዎች የተሟሉለት ሱፐርማርኬት ሲሆን፤ በቅርንጫፉ የኤልፎራ ምርቶች የሆኑና ሌሎችንም የሀገር ውስጥና የውጭ ምርቶችን በመሸጥ ላይ ይገኛል።

great contribution and continued commitments towards

expanding companies business, creating job opportunities

and providing customers with quality and standard products

and services.

W/ro Tahsas Wondimneh, Queens Supermarket General

Manager on her part said that following a decision made

by the CEO, the new supermarket branch is launching its

business with an outlay of three million birr. It has also

created jobs for 15 permanent employees.

The branch has product preparation section and packaging

unit over and above the retail shop which is equipped with

modern machinery to sell ELFORA and other local and

imported products.

ሱፐርማርኬቱ ሲጐበኝ

ሲኢኦ ዶ/ር አረጋና የኩዊንስ ሱፐርማርኬት ሠራተኞች የቡድን ፎቶ

Page 5: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

5

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

University conducted 11th annual multidisciplinary research conference

The 11th Annual Multidisciplinary conference of Unity University (UU) was conducted at Mechare Meda Corporate Conference hall on 15 June 2012.

Speaking at the conference Unity University President and MIDROC Ethiopia CEO. Dr. Arega Yirdaw said that the objective of multidisciplinary research is to open a forum for releasing research outputs, participate in the efforts of sharing information generated by researchers, create a think tank among the academic circle, and help in providing practical solutions to certain problems in the country.

The president also said that it is very important to involve the academia in identifying actual problems observed in the real situation to enable them play their due role in the national development drive.

He further said: “Dissemination and enhancement of ideas to help shape our society and participate in coping with prevailing and emerging problems is something that we should take seriously. In view of this, conducting research is expected to become one of the corner stone’s of our university.”

Thiry-two research papers, categorized under five general themes that included Agriculture and Food Security, Education and Society, Economic Growth and Investment, Mass Media and Society, Environment and Sanitation as well as some topics of cross-cutting issues presented by mostly young and a few veteran scholars.

Over 170 participants drawn from government and non-government higher institutions, Universities, organizations, and MIDROC Ethiopia Technology Group Companies attended the two day conference.

UU Conducted Effective Communication & Team Dynamics trainingExecutive Training on Effective Communication and Team Dynamics organized by Unity University took place from July 16 - 20, 2012, at Unity University Gerji Campus.

The four day training program included effective communication and team dynamics and other wide range of related issues.

The courses were presented by Ato Teshome Bekele, instructor of UU, Ato Desta Asfaw, vice president university resources management services and Ato Tariku Bisrat, vice

president undergraduate studies and special programs of UU respectively.

The training was formally closed by Dr. Brhanue Sisay, Deputy president of UU. He elaborated the purpose of the training.

36 participants took part at the training from the MIDROC Ethiopia Technology group companies including the office of the CEO.

Partial view of participants at multidisciplinary conference

Dr. Birhanu Sisay, Deputy president of UU while speaking at the training

Page 6: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

6

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

የኮምቦልቻ ብረታ ብረት ምርቶች ኢንዱስትሪ የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የማዕረግ

ተሸላሚ ሆነ

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በሀገራችን ለሁለተኛ ጊዜ ባዘጋጀው የ2003 ዓ.ም. መርሀ ግብር በአምራች ድርጅቶች ዘርፍ ተሳታፊ ከነበሩት መካከል የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኩባንያዎች አባል የሆነው የኮምቦልቻ ብረታ ብረት ምርቶች ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግል ማኅበር በማዕረግ ተሸለመ፡፡ የዘመናዊ ሕንፃ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግል ማኅበርም የአድናቆት የምሥክር ወረቀት አግኝቷል።

መጋቢት 30 ቀን 2004 ዓ.ም. በሒልተን ሆቴል በተካሄደው ልዩ ሥነ-ሥርዓት ላይ ሽልማቱንና የምሥክር ወረቀቱን ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ከአቶ ካሣ ተክለብርሃን እጅ የተቀበሉት የኩባንያው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰሎሞን ጌቱ ሲሆኑ፤ ኩባንያው ለግምገማ በቀረበው ሰባት መሠረታዊ የጥራት መለኪያ መስፈርቶች ተገምግሞ ባሳየው የላቀ ተግባር መሸለሙ ተገልጿል።

በሽልማቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የሀገሪቱ አምራችና አገልግሎት ሠጪ ድርጅቶች ዓለም አቀፍ ገበያው የሚፈልገውን ምርትና አገልግሎት በጥራት ማዘጋጀት ከቻሉ በዓለም ላይ ያለንን ቦታ በማስፋፋት የሀገራችንን ዕድገት እውን ማድረግ እንችላለን ብለዋል፡፡

አቶ ኃይለማሪያም አያይዘውም ‹‹ለለውጥ ቁርጠኛ ፍላጐት በማሳየት በውድድር ሂደቱ ለተሳተፋችሁ ሁሉ አድናቆቴን እየገለጽኩ ተሸላሚዎችም እንኳን ደስ አላችሁ›› በማለት ደስታቸውን ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ቦርድ ሰብሳቢና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አድማሱ ፀጋዬ በበኩላቸው በውድደሩ በሥራ አፈፃፀማቸውና ውጤታማነታቸው ጥራትን ወጥነት ባለው መልኩ አጉልተው በማሳየት ብልጫ በማግኘታቸው ድርጅቶቹ አሸናፊ መሆናቸውን ገልፀው፤ ለሽልማት ያበቃቸውም አሠራራቸው ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ያሟላ መሆኑ ስለታመነበት ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የኮምቦልቻ ብረታ ብረት ምርቶች ኢንዱስትሪ፣ መቀሌ ዩኒቨርስቲና ቤቴል ቲቺንግ ሆስፒታል የሁለተኛ ደረጃ የማዕረግ ተሸላሚ ሲሆኑ፤ ዳሸን ቢራ፣ ቃሊቲ ብረታ ብረት ፋብሪካ፣ ኮምቦልቻ ጨርቃጨርቅ አክሲዮን ማኅበር፣ ቢሾፍቱ ሆስፒታል፣ ሐረር ቢራና ብሩህ ተስፋ የመስኖ ውሃ ቴክኖሎጂ የአንደኛ ደረጃ የማዕረግ ተሸላሚ ሆነዋል።

በውድድሩ ለመሳተፍ 150 ድርጅቶች ፍላጐት ያሳዩ ቢሆንም፤ የተሳተፉት ግን 52 ድርጅቶች መሆናቸው ታውቋል። በሽልማቱ ሥነ-ሥርዓት ላይ ሚኒስትሮች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

KOSPI P.L.C and MBI P.L.C. Received Awards

Kombolcha steel products Industry P.L.C (KOSPI), a member of MIDROC Ethiopia Technology Group, received an award for quality in a ceremony held at the Hilton Hotel in the procence of Ethiopia’s Deputy Prime Minister and Minister of Foreign Affairs Hailemariam Desalegne on April 8, 2012.

The Excellence awards were given to nine service rendering organizations including KOSPI P.L.C. and Modern Building Industry P.L.C. (MBI) in recognition of their performance quality in terms of meeting national and international standards.

Handing over the awards to the institutions, Deputy Prime Minister and Foreign Affairs Minister Hailemariam Desalegne said manufacturs and service providers need to develop and enhance quality to become competitive on the global market.

He said that the nation is striving to enhance competence and help local producers to take part in the global market.

The Ethiopian Quality Award Organization (EQAO) Board Chair-person and Addis Ababa University President, Admasu Tsegaye on his part said EQAO has been striving to strengthen quality and system of production in domestic institutions.

EQAO Managing Director, Michael Melaku on his part said 20 producers, 6 construction organizations and 14 non-profit service providers have participated in the competition.

Biruh Tesfa irrigation and water technology, Bishaftu Hospital, Dashen Brewery, Harar Brewery, Kality Metal Factory, Kombolcha Textile S.C, Betel Teaching Hospital and Mekele University were also the recipients of merit awards.

የኤም.ቢ.አይ. ሥራ አስኪያጅ ሽልማቱን ሲቀበሉ

የኮስፒ ሥራ አስኪያጅ ሽልማቱን ሲቀበሉ

Page 7: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

7

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

ለታሪካዊ እሴቶቻችንና ቅርሶቻችን ትኩረት ይሰጥ

የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ የማኔጅመንትና የሠራተኛ ተወካዮች እንዲሁም በቺፍ ኤግዝኪዩቲቭ ኦፊሰር ቢሮ ስር ከሚተዳደሩ 20 የሚጠጉ ድርጅቶች የተውጣጡ ሠራተኞችን በአጠቃላይ 90 /ዘጠና/ የሚሆኑ አባላትን ያካተተ ቡድን በአማራ ክልል የሚገኙ ቀደምት ታሪካዊ ቦታዎችን፣ እጅግ አስደናቂ የሆኑ አብያተ-ክርስትያናትንና መዘክሮቻቸውን እንዲሁም ከሥራ ጋር የተያያዙ ተቋሞችን ከግንቦት 18 - 26 ቀን 2004 ዓ.ም. ጐብኝቷል። የሚድሮክ ኢትዮጵያ ሲኢኦ ዶ/ር አረጋ ይርዳው በዚህ ጉብኝት ላይ በአጠቃላይ ያስተዋሉትን መነሻ በማድረግ ለባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር በደብዳቤ ያቀረቡት ሃሳብ እንደሚከተለው አቅርበዋል፡፡

‹‹በአማራ ክልል ባደረግነው ጉብኝት በቱሪስት መስህብነትና በታሪካዊ መዘክርነታቸው ዓለምን ያስደነቁ ቅርሶቻችን የታሪክና የሥነ-ጥበብ አለኝታ ከመሆናቸውም ባሻገር ሊጐበኟቸው በሚመጡ ቱሪስቶች እና ተመራማሪዎች ዘንድ ስለሀገራችን ከፍተኛ ግምት እንዲሰጡ የሚያደርጉ መሆናቸውን የበለጠ ለመገንዘብ ችለናል፡፡ ከዚህም ባሻገር የሀገራችንን የቱሪዝም ገቢ እንደሚያጠናክሩም እሙን ነው፡፡››

‹‹በተለይም ዛሬ ዓለም በተቀራረበበትና የተለያዩ የቱሪዝም አቅጣጫዎች በበዙበት ወቅት ሀገራችን ጥሩ መሠረት ያላት በመሆኗ ለእሴቶቻችን ከፍተኛ ግምት በመስጠት የበለጠ ተጠቃሚ እንድንሆን

እድል ከመስጠቱም በላይ ከሌሎችም ሀገሮች ጋር ተፎካካሪ ሊያደርገን ይችላል፡፡››

‹‹ይህን በጉብኝታችን የተመለከትናቸው እጅግ አስደናቂ የታሪክና ቀደምት የሃይማኖት ቦታዎች እንዲሁም ቅርሶች በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ መሆናቸውን ለመታዘብ ችለናል፡፡›› ለምሳሌ

- በላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስትያናት የውኃ ፍሳሽና የመሰንጠቅ ሁኔታ፤

- በጐንደር፣ ደብረብርሃን ሥላሴ ቤተክርስትያን እና በጣና ሐይቅ ደሴት በምትገኘው ኡራ ኪዳነምሕረት የሚታዩት ሥነ-ሥዕሎች እየተበላሹ ቀለማቸው እየተለወጠ፣ እየደበዘዙ፣ እየተቀደዱ፣ በከፊልም እየተቆረጡ የሚታዩ መሆናቸው ተጠቃሽ ናቸው፡፡

“ በመሆኑም ለእነዚህ የማንነታችን መገለጫ ለሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ታሪካዊ እሴቶቻችን ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ተገቢውን እንክብካቤና ጥበቃ የሚያገኙበት አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ በአክብሮት ለማስገንዘብ እንወዳለን፡፡ ” በማለት ዶ/ር አረጋ ለታሪካዊ ቅርሶች ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው የበኩላቸውን ሀሳብ አቅርበዋል፡፡

የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ኩባንያ ሴት ሠራተኞች ‹‹ሴቶችና ካንሰር›› በሚል አብይ ርዕስ በመቻሬ የሠራተኞች የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለሁለተኛ ጊዜ በባለሞያ ትምህርታዊ ገለፃ ተደረገላቸው፡፡ በዚሁ በአዲስ አበባ ባሉ የቴክኖሎጂ ግሩፑ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሴት ሠራተኞች በተሣተፉበት ትምህርታዊ መድረክ ላይ ትምህርቱን የሰጡት የመቻሬ ክሊኒክ ጋይናኮሎጂስት ዶ/ር ሰላማዊት አሻግሬ ናቸው፡፡

ዶ/ር አረጋ ይርዳው፣ በወርሃዊ የስብሰባ ፕሮግራም ላይ ባደረጉት ንግግር በዓለማችን እንዲሁም በሀገራችን ለበርካታ ወገኖች ሕልፈትና ለስቃይ በመዳረግ አሳሳቢ ደረጃ ስለደረሰው ካንሰር በቂ ግንዛቤ እንዲኖርና ራስን ከበሽታው ለመከላከል እንዲቻል ተከታታይ የሆነ የትምህርት መድረክ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ጠቁመዋል። በተለይም ከባዮሎጂካል አፈጣጠር ጋር በተያያዘ ሴቶችን በይበልጥ የሚጋለጡበት በሽታ ላይ በባለሙያ ትምህርት መስጠቱ ሴቶች

ካላቸው የላቀ ሚና አንጻር ህብረተሰቡን እንደመታደግ እንደሚቆጠር አጽንኦት ሰጥተውታል፡፡ ሁለተኛው የትምህርት መድረክ ሴቶች ብቻ እንዲገኙ የተደረገው በግልፅ ሀሳባቸውን እንዲለዋወጡ አመቺ መድረክ ለመፍጠር መሆኑን ሲኢኦ ገልፀዋል፡፡

በቅድመ ካንሰር ምርመራ ላይ የካበተ ልምድና ስልጠና ያላቸው ዶ/ር ሰላማዊት አሻግሬ በመጀመሪያውና ወንድ ሠራተኞች ጭምር በተገኙበት ትምህርት መድረክ ላይ በማህፀን ካንሰር ላይ ትምህርት የሰጡ ሲሆን፤ በሁለተኛውና ሴቶች ብቻ በተገኙበት ስብሰባ ላይ በጡት ካንሰር ላይ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡ ይህን ትምህርት በማዘጋጀት ረገድ የመቻሬ ከፍተኛ ክሊኒክ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር አለባቸው ኃይሉ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡

በስልጠናው ላይ የተካፈሉት የቴክኖሎጂ ግሩፑ ሠራተኞች ልዩ ልዩ ጥያቄዎችን ለዶ/ር ሰላማዊት በማቅረብ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡

ትምህርታዊ ሥልጠናው ሲሰጥ

ለሴት ሠራተኞች በካንሠር ላይ ትምህርት ተሰጠ

Page 8: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

8

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

የዜግነት ኃላፊነት ለመወጣት - Corporate Citizenship

UNDP ለትረስት ሠራተኞች ምሥጋና አቀረበ• ዮናይትድ ኔሽን ዴቨሎፕመንት ፕሮግራም ለትረስትና የሰው ኃይል አገልግሎት በላከው የምሥጋና ደብዳቤ እንደገለጸው አቶ መክብብ መራዊ፣ አቶ ዳኛቸው ታደሰ እና አቶ ትዕግእቱ ሙላት በኢሬክስን ሕንጻ ውስጥ የዩ.ኤን.ዲ.ፒ ሠራተኛ ንብረት የሆነና ጠፍቶ ያገኙትን ላፕቶፕ ኮምፒውተር ለድርጅቱ በታማኝነት በማስረከባቸው ዩ.ኤን.ዲ.ፒ ለሠራተኞቹ ያለውን አድናቆት እንዲህ በማለት ገልጿል። ‹‹የኩባንያዎቻችሁ አባል የሆኑት እነዚህ ሠራተኞች ታማኝነትና ቅንነት የተላበሱ በመሆናቸው እጅግ ሊደነቁ ይገባል፡፡ እኛም ከልብ የሆነ አድናቆታችንንና ምሥጋናችንን እንገልፃለን፡፡››

"Thank You for your loyalty." • United Nations Development Programm (UNDP) wrote apperciation letter for Trust P.L.C. employees for their honesty, integrity and loyality for what they perform in Ericson building while they were on duty. The letter reads as follows.I want to take this opportunity to express my appreciation for three staff members of your organization, Mr. Mekbib Merawi, Mr. Daganchew Tadesse and Mr. Tigistu Mulat, who found a lost laptop computer of a UNDP Staff member at the Ericsson Building on 21 May 2012 and returned it to the owner. Working in your organization requires honesty, integrity and personal probity. I rate your staff members highly on all these attributes. Heartfelt thank you for them on their commitment and dedication.

ሚድሮክ ወርቅ በጉጂ ዞን ለሚገኙ ሁለት ወረዳዎች የልዩ ልዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ • የሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኩባንያ የሚያስተዳድረው የለገደንቢ የወርቅ ማዕድን በጉጂ ዞን ለሚገኘው ለኦዶ ሻኪሶ ወረዳ ፍርድ ቤት 4 ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተሮች ከነሙሉ አክሰሰሪዎቻቸው እና ለሰባቦሩ ወረዳ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ለመማርና ማስተማር የሚረዱ ልዩ ልዩ የቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ።ርዳታው የተበረከተው ዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ኦፊሰርና የሚድሮክ ወርቅ ዋና ሥራ አስኪያጅ ለሥራ ጉብኝት በአካባቢው በተገኙበት ወቅት በኦዶ ሻኪሶ ወረዳ አስተዳደር ልዩ ልዩ ሴክተር መ/ቤቶች ከተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ያደረጉትን የጋራ ውይይት መነሻ በማድረግ እና በቀረበላቸው የድጋፍ ጥያቄ መሠረት ነው።በቅርቡ በኦዶ ሻኪሶ ወረዳ ፍርድ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በተካሄደ ሥነ-ሥርአት ሚድሮክ ያበረከተውን የኮምፒውተሮች ድጋፍ የኩባንያው ተወካይና የሕዝብ ግንኙነት ሱፐርቫይዘር አቶ በላይ ተስፋዬ ለፍርድቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሐብታሙ ነጋሣ አስረክበዋል። ፕሬዚዳንቱም ባደረጉት ንግግር ፍ/ቤቱ የሚሰጠው የፍትህ አገልግሎት በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ግልፅና ዘመናዊ እንዲሆን ኮምፒውተሮቹ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርጉ በመጥቀስ

ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ የኩባንያው ተወካይ አቶ በላይ በበኩላቸው እንዳሉት የኮምፒውተር ድጋፍ በመደረጉ የፍትህ ውሳኔ አሰጣጡን ዘመናዊና ጥራት ያለው እንደሚያደርገው እምነታቸውን ገልፀዋል።በሌላ በኩል የሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኩባንያ በጉጂ ዞን ደቡባዊ ጫፍ ላይ አዲስ የተመሠረተው ሰባቦሩ ወረዳ ካሉት ት/ቤቶች አንዱ ለሆነው ጨሪ በቀቃ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት እያንዳንዳቸው ከ3 - 4 ተማሪ ማስቀመጥ የሚችሉ 40 ደረጃቸውን የጠበቁ የት/ቤት ዴስክ ወንበሮችን አሰርቶ ለት/ቤቱ ርዕሰ መምህር አስረከበ፡፡ዴስኮቹን በኩባንያው ተሽከርካሪዎች በማጓጓዝ ልዩ ስሙ ‹‹በቀቃ ቦሼ›› በሚባል ሥፍራ በደረሱበት ወቅት የአካባቢው ነዋሪዎች የአገር ሽማግሌዎች የሃይማኖት አባቶችና ቁጥራቸው ከ500 በላይ የሚገመት የት/ቤቱ መምህራንና ተማሪዎች በታላቅ እልልታና ሆታ ተቀብለውታል። በት/ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት ዴስኮቹን ለት/ቤቱ ርዕሰ መምህር ለመ/ር ተካልኝ ሽብሩ ሮባ ያስረከቡት አቶ ተስፋዬ ቀጄላ በኩባንያው የህዝብ ግንኙነት ቢሮ የማህበረሰብ ጉዳዮች ኦፊሰር ናቸው፡፡

ለሻኪሶ ወረዳ 2ኛና ደረጃ መሰናዶ ት/ቤት ለተሰጠው የጉብኝት ዕድል ምሥጋና እናቀርባለን• ድሪባ ጉተታ

ከሻኪሶ ወረዳ 2ኛና መስናዶ ት/ቤት የወላጅ የመምህራን ህብረት ኮሚቴ ሰብሳቢበሚድሮክ ኢትዮጵያ ባለሀብትና ሊቀመንበር በሆኑት በሼክ ሙሐመድ ሁሴን አሊ- አልአሙዲ መልካም ፈቃድ እንዲሁም በሚድሮክ ኢትዮጵያ ሲኢኦና በሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አረጋ ይርዳው መልካም አስተዳደር ሻኪሶ ወረዳ 2ኛና መሠናዶ ት/ቤትን በተለያዩ ጊዜያት ስለተደረገው ከፍተኛ ዕርዳታ ምሥጋናችንን እናቀርባለን፡፡ በቅርቡም ለመሠናዶ ት/ቤት ተማሪዎች ከፍተኛ ወጪ በማውጣት በሀገርህን ዕወቅ ትምህርታዊ ፕሮግራም እንዲሳተፉ በመደረጉ የተሰማንን ደስታ እንገልፃለን፡፡

በጉብኝቱ የተሳተፉት ተማሪዎች ከሰኔ 20-23 ቀን 2004 ዓ.ም. ለ177 /አንድ መቶ ሰባ ሰባት/ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ሙሉውን የጉዞ ወጪ ከሻኪሶ አዲስ አበባ ደርሶ መልስ በማዘጋጀት ደረጃቸውን በጠበቁ የዋቢሸበሌና አክሱም ሆቴሎች የምግብና የመኝታ መስተንግዶ እንዲያገኙ በማድረግ እንዲሁም በዘመናዊ የሬንቦ መኪናዎች በመገልገል የተሳካና ኃላፊነት የተሞላበት ታሪካዊ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ ተማሪዎቹ ወደ መጡበት በሠላም እንዲመለሱ ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ በማድረግ ትውልድ የማይረሳው ታላቅና አኩሪ ሥራ እና የላቀ የትምህርት ድጋፍ ተደርጐልናል፡፡ ብለዋል አቶ ድሪባ ጉተታ።

ለዚህ ሁሉ መነሻና ምክንያት ለሆኑን ክቡር ዶ/ር ሼክ ሙሐመድ አሊ አል-አልሙዲን፣ ለዶ/ር አረጋ ይርዳው እና በዚህ ዘመናዊና አስተዳደር ሥር ለሚገኙ የሲኢኦ የሚድሮክ ወርቅ፣ እና የሬንቦ ማኔጅመንትና ሠራተኞች የላቀ ልባዊ ምስጋናችንን በወከለን ህዝብና በት/ቤቱ ማህበረ-ሰብ ስም እናቀርባለን፡፡

ከዚህም ሌላ ባለፉት ዓመታት በሚድሮክ ወርቅ ማዕድን ኩባንያ ከተደረጉልን ድጋፎች ውስጥ ዋና ዋናዎችን እንደሚከተለው እንጠቅሳለን በ1998 ዓ.ም. የመሰናዶ ትምህርት ለመክፈት የበጀት እጥረት በገጠመን ጊዜ አሥራ ሰባት /17/ ኮምፕውተሮችን ከነፕሪንተሮቻቸው በመርዳት በሻኪሶ የመሠናዶ ት/ቤት መከፈት ብዙዎች የትምህርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል። ዘመናዊ ቤተ መጽሐፍት ሲገነባ ከፍተኛ ድርሻ የያዘ ገንዘብ ለግንባታው /1.15 ሚሊዮን ብር/ በመረዳት ስኬታማ ድጋፍ ተደርጐልናል፡፡ ለት/ቤቱ በቋሚነት ሁለት አትክልተኞችን በመቅጠር የግቢው ውበት እንዲጠበቅ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ለዚህና ለሌሎች ስለተደረጉልን በርካታ ድጋፍና እገዛ ምሥጋናችንን እንገልጻለን፡፡

በኢትዮጵያዊነቴ እንድኮራ ያደረገኝ የማይረሳውን ረጅሙ ጉዞ • የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ሠራተኞች ያደረጉትን የሀገርህን ዕወቅ ጉዞ በማስመልከት በርካታ የምሥጋና ደብዳቤ ደርሶናል፡፡ ከዚህ መሀል ለአብነት ያህል የአቶ ወርቁ ዘውዴን መልዕክት አጠር አድርገን እንደሚከተለው አቅርበነዋል ‹‹በመጀመሪያ የሀገር ኩራትና የወገን አለኝታ በሆኑት ብርቅዬው የሀገር ልጅና በታላቁ ኤንቨርስተር ድርጅት ተቀጥሬ በመስራቴ እድለኛ መሆኔን እገልፃለሁ።በተለይም ምቹ ከሆነ ሀገርና ከተደላደለ ኑሮ ላይ የሀገርንና የወገንን ውለታ ለመክፈል ያካበቱትን እውቀትና ልምድ ሰንቀው በመምጣት ሰው ተኮር የሆነ ፖሊሲ ቀርፀው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ አቋቁመው መልካም አስተዳደራቸው በሀገር ደረጃ በአርያነቱ ወደር ያልተገኝለት የሥራ መሪ በሚያስተዳድሩት ኩባንያ ተቀጥሬ በመስራቴ እጅግ በጣም እኮራለሁ፡፡ድርጅታችን አድጎና ገቢአችን ተሻሽሎ ጥሩ ኑሮ እንድንኖር ከሚያደርጉልን ድጋፍ በተጨማሪ ሀገራችንን እንድናውቅና የስልጣኔ ምንጭ መሆናችንን እንድናምን በየዓመቱ በሚካሄዱት የሀገርህን እወቅ ፕሮግራም የዘንድሮው ተሳታፊ በመሆኔ ደስታዬን እገልጻለሁ::››

ወርቁ ዘውዴሰሚት ኢንጂነርድ ሠራተኞች ማህበር፣ ሊቀመንበር

ምሥጋና

Page 9: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

9

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

ትናንት

እትብታቸው የተቀበረው ጎንደር ነው፡፡ ያውም ፋሲል ግንብ አጠገብ ልዩ መጠሪያው እንኮዬ መስክ የተባለው ቦታ፡፡ ጎንደር ብዙ አልቆዩም። ገና የኔታ ት/ቤት ተማሪ ሳሉ ነበር ወደ ወልዲያ ከተማ ያቀኑት። እናም የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ጣይቱ ብጡል ት/ቤት ወልዲያ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ወ/ሮ ስህን ደሴ፣ የኮሌጅ ትምህርታቸውን (በእርሳቸው አባባል) መሀንዲስ ኮሌጅ አዲስ አበባ አከናውነዋል፡፡

እኚህ ሰው ማናቸው ሰውዬው የዋዛ እንዳይመስሏችሁ፡፡ የኮሌጅ ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ (እርሳቸው ሲገልፁ አራት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ ስድስት ኪሎ እያሉ ነው) ካጠናቀቁ በኋላ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ለማግኘት ወደ እንግሊዝ አቅንተዋል፡፡ ከምህንድስና ሙያው ፊታቸውን መለስ አርገው የአመራር ሙያን ለመቅሰም ደግሞ ወደ አሜሪካ፡፡ ዛሬም አላረፉም የመሪነት ሚናቸውን ለማጠናከር ‹ሊደርሺፕ ኤንድ ቼንጅ› በሚል ሙያ በትምህርቱ መስክ ለመመረቅ አንድ ዓመት ከምናምን ይቀረኛል ይላሉ፡፡

እኚህ መማር በቃኝ የማይሉ ሰው ማናቸው የኮሌጅ ትምህርታቸውን አጠናቀው በቅድሚያ በቅጥር ‹‹ሀሌታ›› ብለው ስራ የጀመሩት በአንጋፋው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነበር፡፡ በመሀል ለሁለተኛ ዲግሪያቸው ወደ እንግሊዝ ከመሄዳቸው ሌላ የወጣትነት ዕድሜያቸውን ፉት ብለው የጨለጡት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውሰጥ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ለአስር ዓመታት፡፡ ወደ አሜሪካ ካቀኑ በኋላም ለሃያ ዓመታት በሥራ ላይ አሳልፈዋል፡፡ እንደገና ከሃያ ዓመታት በኋላ ወደ አገራቸው ተመልሰው ደግሞ እነሆ በሥራ ላይ ለ12 ዓመታት፡፡ በድምሩ ለ42 ዓመታት በሥራ ያሳለፉት እኚህ ልበ ደንዳና ማናቸው ማታ ማታ በማስተማር - ቀን ቀን በኮሌጅ በመማር ገና በለጋነት ዕድሜያቸው ከሥራ ጋር መጨባበጣቸውን ሲገልፁና የ42 ዓመት የሥራ ዘመናቸውን የተነበበ መፅሀፍ ወደኋላ ሲገልጹ ትናንትን የዛሬ ያህል በማስታወስ ነበር፡፡

ዛሬእኚህ ሰው ዛሬ የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ናቸው፡፡ ሰውዬው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ባለሃብት ከሆኑት ከሼህ መሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲን ቀጥሎ በሚድሮክ ውሰጥ ስማቸው የገነነው ዶ/ር አረጋ ይርዳው ናቸው፡፡

ዶ/ር አረጋን ላለፉት 12 ዓመታት በሚገባ አውቄያቸዋለሁ። አብሬያቸውም ሰርቻለሁ የሚሉን የሚድሮክ ኢትዮጵያ የሰው ሀብት ልማት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ፍሬህይወት ዕንቁሐዋርያት ናቸው፡፡ እናማ ዶ/ር አረጋን እንዴት ይገልጿቸዋል ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ሲመልሱ ዶ/ር አረጋን በብዙ መንገድ መግለፅ ይቻላል ብለው ይጀምራሉ፡፡ ‹‹ዶ/ር አረጋን በብዙ መንገድ መግለፅ ይቻላል፡፡ አለቃ ናቸው፣ አባት ናቸው፣ ቤተሰብ ናቸው። በሁሉም ሰው ሕይወት ውስጥ ጠልቀው የሚገቡ አባት ናቸው። ሁለገብነታቸው ይጎላል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሠራተኛ ቢታመም ቤቱ ድረስ ሄደው እስከመጠየቅና ከኪሳቸው አውጥተው እስከመርዳት የሚዘልቁ ናቸው፡፡›› ይላሉ ወ/ሮ ፍሬህይወት፡፡

ዶ/ር አረጋን ከሌላው የተለየ ያደርጋቸዋል ብዬ የማስበው ላንተ የሚሰጥህንና የሚገባህን ብቻ ሳይሆን ከሚሰጥህና ከሚገባህ በላይም መደረግ አለበት ብለው የሚያምኑ መሆናቸውን ነው የሚለው ደግሞ በሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ የዋንዛ ፈርኒሺንግስ ኢንዱስትሪ እና የመሠረታዊ ሠራተኛ ማህበሩ ሊቀመንበር የሆነው አቶ እታለማሁ አዳሙ ነው፡፡ ጉዳዩን በደንብ ሲያብራራውም ‹‹አንድ ሰው መብቱ እዚህ ጋር አለ እንበል፡፡ ሆኖም ከመብቱ በላይ ቢያልፍ ምን ችግር አለው ብለው የሚከራከሩ ናቸው፡፡›› ይላቸዋል፡፡ የብዙዎች የመሪነት ሥርዓት ሥራ ተኮር ነው ይባላል የዶ/ር አረጋ ግን ሰው ተኮር ነው ይላል አቶ እታለማሁ፡፡

ፍለጋዝነኛው ባለሃብት ሼህ መሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲን ደሴ ተወልደው ያደጉት ወልዲያ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዶ/ር አረጋ ደግሞ ጎንደር ተወልደው ወደ ወልዲያ ዘልቀዋል፡፡ ወልዲያ እነዚህን ሁለት ብላቴናዎች ያገናኘች ድልድይ ትሆንና ከልጅነት እስከ ወጣትነት አብረው ያሳልፋሉ፡፡

‹‹የሕይወት ጉዳይ ሆነና ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት በኋላ እኔና መሐመድ ተለያየን›› የሚሉት ዶ/ር አረጋ ‹‹ሼህ መሐመድ ከኢትዮጵያ አልፈው እስከ ሳዑዲ አረቢያ በመዝለቅ ዛሬ አንቱታ ያተረፉበትን የባለሃብትነት ተግባር በንግድ ሲያጠናክሩ እኔ ደግሞ ከትምህርት ጋር ይበልጥ ለመዋሀድ እስከ አሜሪካ ዘለቅሁ፡፡›› ይሉናል፡፡ ሁለቱም በየተሰማሩበት መትጋታቸውን ዛሬ ያሉበት ደረጃና ስብዕናቸው ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ኋላ ላይ ሼሁ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያከናውኗቸው ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት እየተጠናከሩና እየበረቱ ሲሄዱ ያን የሚያቀናጅላቸው ሁነኛ ሰው ማለም ብቻ ሳይሆን ማሰስም ይጀምራሉ፡፡ አስሰው አስሰው የፍለጋ ታንኳቸው በመጨረሻ ይሳካላቸውና መልህቃቸውን ዶ/ር አረጋን በማግኘት ይጥላሉ፡፡ ገና ከጨቅላነት ጊዜ ጀምሮ ከልብ የተዋሃደ መቀራረብ ነበራቸውና በመስማማት ይደመደማል፡፡

የዶ/ር አረጋ ወደ ትውልድ አገራቸው መመለስና በተለይ የሚድሮክ ኢትዮጵያን ቢዝነስ ግሩፕ የመገንባት አካሄድ እንዲሁ አልጋ በአልጋ የተከናወነ አልነበረም፡፡ እናም ሼህ መሐመድ ዶ/ር አረጋን ፈልገው ካገኟቸው በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ እያከናወኗቸው ስላሉት የንግድ ስራዎች ዝርዝር አድርገው አወጓቸውና ብትረዳኝስ የሚል ጥያቄ አቀረቡላቸው፡፡ ዶ/ር አረጋም በጉዳዩ ይስማሙና አሜሪካን ሀገር የመጨረሻ ልጄ በትምህርት ላይ ነችና እሷን እስከማስመረቅ ታገሰኝ ይሏቸዋል፡፡ በተጨማሪም ወደ ኢትዮጵያ ተመልሼ ሼሁ የጀመሯቸውን ስራዎች ማጥናት እንዳለብኝም ወሰንኩና ለሰባ ቀናት ያህል በኢትዮጵያ ተዘዋውሬ ኩባንያዎቹንና የተለያዩ አካባቢዎችን አጥንቼ ሮድ ማፕ አዘጋጀሁ ይላሉ፡፡ ሮድ ማፑን ያዘጋጀሁት ኢትዮጵያ ውስጥ ስመጣ በምን ዓይነት መንገድ ምን ልሰራ እችላለሁ በሚል ነበር ያሉት ዶ/ር አረጋ ይህም ለስራው መጨነቄን አመላካች ነበር ብለዋል፡፡

የጥምረቱ ፍልስፍና ዶ/ር አረጋ ባደረጉት ጥናት መሰረት ሼህ መሐመድ በተለያዩ የንግድ ዓለማት ላይ መሰማራታቸውን አረጋገጡ፡፡ እናም ማድረግ የሚገባቸው ይህን የተለያየ የሥራ ዓለም በየራሱ በየሴክተሩ (በየዘርፉ) ማጠናከርና በጥምረት መምራት ወይም በአንድ መምራት የሚል ፍልስፍና ይነድፋሉ፡፡ ‹‹ዛሬም በዚህ ፍልስፍና አምናለሁ›› ይላሉ ዶ/ር አረጋ፡፡

‹‹የጥምረቱን ፍልስፍና ለመተግበር ከእርሻውም ከኢንዱስትሪውም አንድ

ገፀ ብዙው የአመራር ጠቢብዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

የዘንድሮውን ሜይዴይ በዓል ምክንያት በማድረግ ጋዜጠኛ መሰለ ገሕይወት ‹‹ሠራተኛ›› በሚል ርዕስ ባዘጋጀው መጽሔት ላይ ‹‹ሞዴል አሠሪ›› በሚል ከዶ/ር አረጋ ይርዳው የሚድሮክ ኤግዚኪዩቲቭ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ኦፊሰርን ቃለ መጠይቅ በማድረግ የሥራና የሕይወት ተሞክሯቸውን ለአንባብያን አቅርቧል። ይህንንም ጽሑፍ እንደሚከተለው አቅርበነዋል!

ዶ/ር አረጋ ይርዳው

Page 10: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

10

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

አምስት የሚሆኑትን ኩባንያዎች ወሰድኩና ስራ ጀመርኩ›› የሚሉት ዶ/ር አረጋ ከዚያ በኋላም በተለያየ ዘርፍ የተሰማሩትን እነዚህን ኩባንያዎች በአንድ አጣምሮ መምራቱ የሚያመጣውን ፋይዳ ሁላችንም በሚገባ ተገነዘብን ይላሉ፡፡ ምክንያቱም በመረዳዳት ላይ ማተኮሩ የበለጠ እንደሚጠቅመን ተረዳን፡፡ ስትገነጣጠል ብዙ የምታጣው ነገር አለ፡፡ በተለይ ባለሃብቱ የሁሉም አንድ ሰው ከሆነና ነገሮች ከአንዱ ኪስ ወደ አንዱ መሆኑን በሚገባ ካጤንህ የጥምረቱን ፍልስፍና በሚገባ ለመተርጎም ዕድሉ አለህ፡፡ ሰዎችን በሚገባ ማሰልጠን ትችላለህ፣ አንዱ ቦታ ላይ ጠንካራና የተለየ ችሎታ ያለው ሠራተኛ ካገኘህ አቅሙንና ችሎታውን ለሌላው እንዲያካፍል ማድረግ ትችላለህ፡፡

ይቀጥላሉ ዶ/ር አረጋ፡፡ ይህ አዲስ ነገር አይደለም በአሜሪካም ሆነ በአገራችን ሆልዲንግ ካምፓኒ የሚባል ነገር አለ፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ካምፓኒ (እንደ ሚድሮክ ዓይነቱን ማለታቸው ነው) በአግባቡ መምራት ከተቻለ ከደህንነት አኳያ፣ ከሠራተኛው ጥቅም አኳያ፣ ዕውቀትን ከማስተላለፍ አኳያ፣ ሥራን ከማስፋፋት አኳያ ማቀናጀቱ የበለጠ ጥቅም እንዳለው በመረዳቴ ሁሉን በማቀናጀትና በማጣመር ሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕን ዕውን አደረግን ብለዋል፡፡

በእርግጥ እዚህ ጋ አያደክምም ወይ የሚል ጥያቄ ሊያስነሳ ይችላል። መልሱ አዎ ያደክማል ነው - የሚሉት ዶ/ር አረጋ ምክንያቱም ዛሬ ስታይ የምትውለው የአንዱን ኮሰስ ያለ ኩባንያ ጉዳይ ይሆናል ነገ ደግሞ በጀቱ 5 ሚሊዮን ብር ስለሆነ ጉዳይ ስታሰላስል ትውላለህ፣ ከነገወዲያ ደግሞ የምትጨነቀው 500 ሚሊዮን ብር በጀት ስላለው ኩባንያ ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም በመሪነት ዓይን ስታያቸው ሁሉም ጋ ያሉት ሠራተኞች - ሠራተኞች ናቸው፡፡ ኩባንያውም ኩባንያ ነው። ስነ ስርዓቱ - ስነ ስርዓት ነው፡፡ ፖሊሲዎቹ ፖሊሲዎች ናቸው፡፡ ዋናው ነገር የአካሄድ ብዛት ሳይሆን አካሄዱን ወጥ ማድረጉ ላይ ነው። በዶ/ር አረጋ አገላለፅ ዩኒፎርም ማድረግ መቻሉ ነው፡፡ እናም በዚህ መልክ ነው ዶ/ር አረጋ የሚድሮክን የጥምረት ፍልስፍና መሬት ላይ ያሳረፉት። አሁን አሁን ‹ግሩፕ› እያሉ የተለያዩ ስራዎችን የጀመሩ ሌሎች ባለሃብቶችና ካምፓኒዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በብዛት እያየን ነው፡፡ በአግባቡ መምራት ከቻሉት ጥሩ ነገር ነው የሚሉት ዶክተሩ ይህንን ጉዳይ በአጭሩ ሲገልጹት ‹‹ምንም የሚከብድ ነገር የለም፡፡ የበረቱ ሰዎች አገር ይመሩ የለ እንዴ እንኳን ኩባንያ›› በሚል ይቋጩታል፡፡

አስተዳደግለዶ/ር አረጋ የአንድ ሰው ማንነት በሚገባ ከሚገለፅባቸው ሁኔታዎች ዋናው አስተዳደጉ ነውና እስቲ ስለአስተዳደግዎት ጥቂት ይበሉን አልናቸው፡፡ የእኔም ሆነ የአለቃዬ (የሼህ መሐመድ) አስተዳደጋችን በጣም ጥሩ የሚባል ዓይነት ነበር ብለው ጀመሩ፡፡ ‹‹በአንድ መንደር ነው ያደግነው፡፡ በአንድ ቃል ከመጠን በላይ ዲሲፕሊንድ በሆነ የቤተሰብ አስተዳደግ ነው ያለፍነው፡፡ አንድን ነገር ለማግኘት ጥረን ግረን መሆን እንዳለበት እናምናለን፡፡ ዝም ብሎ ከሰማይ መና መጠበቅ ከንቱ እንደሆነ እየተነገረን ነው ያደግነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ያለ አባት እሱ ቆንጆ ጫማ ማድረግ ያማረው ከሆነ ለልጁም የዚያው ዓይነት ይገዛል፡፡ ያ ደግሞ ልጁ አባቱ እንደገዛው ዓይነት ጫማ ለመግዛት አንዳይጥርና እንዳይለፋ ያደርገዋል፡፡ ብዙ ውጣ ውረድ በሕይወት ውሰጥ እንዳለ እንዳይረዳ ይጋርድበታል፡፡ ምክንያቱም ሳይለፋ ሳይደክም በአቋራጭ በአባቱ በኩል አግኝቶታልና፡፡›› ይላሉ፡፡‹‹እኛ ግን›› አሉ ዶ/ር አረጋ ‹‹እኛ ግን ሌሎች የታላላቆቻችን ነገር እያየን፣ አድጌ እዚያ ቦታ ደርሼ እንደ እገሌ የዚያ ዓይነት ጫማ አድርጌ ባየሁ እያልን እየተመኘን ነበር ያደግነው፡፡ በጣም ዲሲፕሊንድ የሆነ አባት አለኝ (በነገራችን ላይ አባቴ አሁንም በሕይወት አለ፡፡ ወደ መቶ ዓመት እየተጠጋ ነው) የአባቴ የሥራ ሰዓት አከባበር፣ ቅንነቱ፣ ለሕብረተሰቡ የሚያደርጋቸው ነገሮች ብቻ ሁሉ ነገሩን ከአባቴ ወስጃለሁ። ያኔ የእኔ ስራ ትምህርት ነበር፡፡ ልክ አባቴ ያደርግ እንደነበረው ጠዋት እነሳና እወጣለሁ፣ ማታም አጠናለሁ ደብተርን ሸፍኖ ንጹህ ከማድረግ ጀምሮ በጥሩ ሁኔታ ትምህርቴን ማከናወኔን እቃኛለሁ፡፡ ይህ ነው አስተዳደጌ›› ይላሉ፡፡ዶ/ር አረጋ በወጣትነታቸው ገና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሳሉ ነበር የእረፍት ጊዜ ይኑረኝ ሳይሉ ወደ ትዳር ዓለም የገቡት፡፡ በትምህርት ዓለም ሳሉ ወደ ትዳር ሕይወት መግባታቸው የበለጠ ኃላፊነት እንዲሰማቸው ምክንያት ሆናቸው፡፡ ከምረቃ በኋላ ወደ ስራው ዓለም ሲቀላቀሉ ኃላፊነቱን ቀደም ብለው ተገንዝበውት ነበርና አልተደናገሩም፡፡ እዚህ ጋ ዶ/ር አረጋ ራሳቸውን የሚገልጹበትን መንገድ እናስቀምጥ፡፡ ‹‹ኃላፊነትን መወጣት ገና በልጅነቴ ከአባቴ ቀሰምኩ፡፡ ከዚያም ዕውቀትና የሥራ ልምድ ተጨመረበት፡፡ ሌሎችን ማየት መጣ፣ መስሪያ ቤት መምራት ተከተለ፡፡ ይሄ ሁሉ ዕድገት ነው፡፡ ‹‹ሌላው ጉዳይ የሕይወት ጉዳይ ነው፡፡ እኔ ሕይወትን የምተረጉመው እያንዳንዱ ሰው ለሌላው ሰው ጥሩ ነገር ለማድረግ መጣር አለበት በሚል ነው፡፡ በሌላው ሕይወት

ላይ እሴት መጨመር ይገባል ባይ ነኝ፡፡ ህይወታችን ላይ ጥሩ አሻራ አሳርፏል የምለው፡፡›› በማለት ገልፀውታል፡፡የዘወትር ተግባርዶ/ር አረጋ ከሠራተኞቻቸው ቀድመው መቻሬ ሜዳ ይደርሳሉ፡፡ (መቻሬ ሜዳ ሣር ቤት አካባቢ ያለው ቢሮዋቸው ነው) ቢሮዋቸውን ከፍተው ይገቡና የሚያስቸኩል ነገር ካለ ፊርማቸውን ያኖሩበታል። ወደ ሁለት ሰዓት ገደማ ሠራተኞቻቸው ከተለያዩ አቅጣጫዎች እየመጡ ከሰርቪስ ሲወርዱ ሜዳው ላይ ወጣ ብለው ይቀበሏቸዋል።ከዚያ ሁሉም ወደ ቢሮዋቸው ሲገቡ ይመለከቱና እግረ መንገዱንም የተለየ ጥያቄ ያለው ሠራተኛ በአጋጣሚ ካገኙ ያስተናግዱና እሳቸውም ወደ ቢሮዋቸው ይገባሉ፡፡ ‹‹የምከተለው ግልፅ አሠራር ነው፡፡ ቢሮዬ ለማንኛውም ሠራተኛ ክፍት ነው›› ይላሉ ዶ/ር አረጋ። እናም በቢሮዋቸው ውስጥ ሆነው በዕቅድ የታቀዱ ስራዎችንና ያለዕቅድ በአጋጣሚ ከባለጉዳይ ጋር በተያያዘ የሚመጡ አቤቱታዎችን ሲመለከቱና መልስ ሲሰጡ ይውላሉ፡፡ የቀን፣ የሣምንት፣ የወር፣ የዓመት የሚባል የሥራ ዕቅድ አላቸው፡፡ዶ/ር አረጋ እ.ኤ.አ በ1970 በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስራ ሲጀምሩ አለቃቸው ፈረንጅ እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ በሂደትም ፈረንጆቹ በሀበሻ እየተተኩ ሲሄዱ እሳቸውም የአለቅነት ወግ ደርሷቸዋል። ከወጣትነታቸው ጀምሮ ስራ ላይ ማተኮራቸውና በውጤት ማመናቸው ለዛሬው ስብዕናቸው እንደረዳቸው ይናገራሉ፡፡ የሥልጠና መሀንዲስ ሆነው ስራ የጀመሩበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ክፉና ደግ ያዩበት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ በስራቸው ላይ አንቅፋት የሚሆን አለቃ ሲያጋጥማቸው በዝምታ እንደማያልፉና ከእርሳቸው በታች ያሉ ሠራተኞች በሌሎች የበላይ አለቆች አላስፈላጊ ወከባ ሲደርስባቸው እያዩ እንደማይታገሱ ሁሉ ያስታውሳሉ፡፡ አንዲያውም ከዚህ ጋር በተያያዘ ከበላይ አለቃቸው ጋር ተሟግተው ከስራ የታገዱበት ጊዜ ሁሉ እንደነበር ትዝ ይላቸዋል፡፡ ከዚያም ሙግታቸው ትክክል መሆኑ ታውቆ ከዕገዳ ነፃ እንደሆኑ ሁሉ ያስታውሳሉ፡፡ ባመንኩበት ነገር ለሠራተኞቼ መከራከር የጀመርኩት ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ስለሆነ አለቆችን ማክበር በሚገባኝ መጠን ማክበር የጀመርኩትም ያኔ ነው ይላሉ፡፡ አለቃ ስለሆነ ካንተ የተሻለ ያውቃል ማለት አይደለም። አለቅነት ዕውቀት ያላቸውን ሰዎች በሚገባ አውቀሀቸውና በስራ ላይ አሰማርተሀቸው በቂ ውጤት እንዲያመጡ የማድረግ ጥበብ ነው፡፡ አሁን ስላለሁበት የአለቅነት ሁኔታ መናገር የሚችሉት ሠራተኞቼ ናቸው የሚሉት ዶ/ር አረጋ ሁለት ዓይነት ሃብት ቢኖርም (አንዱ ሰው - አንዱ ቁሳቁስ) ‹‹በእኔ እምነት ግን የማንኛውም ድርጅት ዋና ሃብት ሰው ነው›› ይላሉ፡፡ ቁሳቁሱን ከሰው የምታስቀድም ከሆነ ችግር አለ የሚሉት ዶ/ር አረጋ ‹‹ስለዚህ የመጀመሪያው ጥረታችን ሠራተኛው ላይ ማተኮር ይሆናል። ሠራተኛው ላይ ማተኮር ማለት ታዲያ አንዳንድ ልወደድ ባይ አለቆች እንደሚያደርጉት ደመወዝ መስጠትና ከረሜላ መወርወር ብቻ አይደለም የሠራተኛውን ስብዕና መጠበቅ፣ ከቤተሰቡ ጋር ያለውን አኗኗር እንዲያስተካክል መርዳት፣ አለሁልህ ማለት፣ ለችግሩ መድረስ፣ የሚገባውን መስጠትና የሚጠበቅበትን ውጤት እንዲያመጣ ማገዝ ሌላም ሌላም፡፡ ይህ ነው የእኔ እምነት፡፡››

ከስድስት ሺ በላይ ሠራተኞችና ከሃያ በላይ ኩባንያዎች በስሬ ስላሉ በእነዚህ ኩባንያዎች ውስጥ ያሉት አለቆችና ሠራተኞች ደግሞ የተለያየ የሕይወት ልምድና ጠባይ ስላላቸው ከሁሉም ጋር በተለያዩ መድረኮች በመገናኘት የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ እሞክራለሁ። ስለእኔም በግልፅ እንዲረዱ በማድረግ እኔም እያንዳንዳቸውን በቅርበት ለመረዳት እሞክራለሁ፡፡

ከሠራተኞቻቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት በምሳሌ ሲገልጹትም ‹‹ማንኛውም ሠራተኛ የእኔ ፊርማ ካላረፈበት ከስራ አይወጣም፡፡›› ይላሉ፡፡ የስድስት ሺ ሠራተኞችን የስራ ውል ማቋረጥ የሚችለው አረጋ ብቻ ስለሆነ ሁሉንም ሠራተኛ በራሱ እንዲተማመን አድርጎታል ይላሉ፡፡ ያ ማለት ግን እነሱም መባረር የለም ብለው እንዲሞላቀቁ አለቃም ማባረር ካልቻልኩ ስልጣኔ ተወስዶብኛል ብሎ እንዲሰጋ በማድረግ አይደለም፡፡ አለቃው ምክንያቱን ዘርዝሮ እገሌ ይባረር ብሎ ፕሮፖዛል ያቀርባል፡፡ እኔም ጉዳዩን እመለከትና በተገኘው ቀዳዳ ሁሉ ይባረር የተባለውን ሠራተኛ ለማዳን እሞክራለሁ፡፡ ሠራተኛውን ለማዳን የሚያስችል ቀዳዳ ካልተገኘና መባረር ካለበት ይባረራል፡፡ ፊርማው ግን የእኔ መሆን አለበት ብለዋል ዶ/ር አረጋ፡፡

ምን ዓይነት ሠራተኛ ይወዳሉ?ዶ/ር አረጋን ከስምንት ዓመት በላይ አውቃቸዋለሁ የሚለው አቶ እታለማሁ እሳቸው ዘመናዊ የማኔጅመንት ሲሰተም ስለመከተላቸውና ማንም ሰው በስራ ዓለም እያለ አለቃው ስራው መሆኑን አበክረው እንደሚመሰክሩ ይናገራል፡፡ በዓመታዊ የደመዎዝ ጭማሪ፣ በቦነስ

Page 11: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

11

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

ጉዳይና በአጠቃላይ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳዮች ላይ ጤናማ ግንኙነት እንዲሰፍን ማድረጋቸው ለሁላችንም ዋስትና ሆኗል የሚለው አቶ እታለማሁ እንዲያውም ለሠራተኞች ሊደረግ የሚገባን ነገር በመቀነስ አትራፊ መሆን አይቻልም የሚል የራሳቸው ጠንካራ ፍልስፍና አላቸው ይላል፡፡

ወ/ሮ ፍሬሕይወት በበኩላቸው የሚማርና ዘወትር ራሱን ማሻሻል የሚወድን ሠራተኛ ያበረታታሉ - ይገፋፋሉ፡፡ በዚህም ብዙ የካምፓኒው ሠራተኞች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡ ፖሊሲው የማይፈቅድላቸው ቢሆን እንኳን በግላቸው እየረዱ ከማስተማር አይመለሱም ይላሉ፡፡ የሚድሮክ ኢትዮጵያ ካምፓኒዎች ድሮ በተናጠል ነበር የሚጓዙት፡፡ አሁን ግን ዶ/ር አረጋ የቡድን መንፈስ እንዲፈጠርና አንዱ ከአንዱ ልምድና ተሞክሮ እንዲቀስም በማድረጋቸው ሁሉም በጋራ እንዲያድጉ በር ከፍተዋል፡፡

ዶ/ር አረጋ የራሳቸውን ስሜት ሲገልፁ ‹‹እኔ የምወደው ሠራተኛ የሕይወቱን ሚዛን ጠብቆ የሚኖር ሠራተኛ ነው›› ይላሉ ሕይወቱን ሚዛናዊ ያደረገ ሠራተኛ ማለት ምን እንደሆነ ሲያብራሩም ሕይወትህ ስራህ ብቻ አይደለም ብለው ይጀምራሉ፡፡ ለእኔ ትክክል ነው ብዬ የማምነው 24 ሰዓት የምታከናውነው ነገር ሁሉ የተስተካከለ ሲሆን ነው ባይ ናቸው፡፡ የሥራ ዓለምማ ራሷን የቻለች ያቺው ስምንት ሰዓት ናት፡፡ ሦስት አራተኛው ሌላ ዓለም ነው፡፡ ቤተሰብ ያላቸው አሉና፡፡ ልጆች ያላቸው አሉና፡፡

የእኔ ሠራተኞች በተቻለ መጠን በትምህርታቸው ላይ ያተኮሩ፣ ለመሻሻል ዋጋ የሰጡ፣ ስለሁኔታቸው፣ ስለውሏቸውና ስለ አለባበሳቸው የሚጨነቁ፣ ራሳቸውን የሚጠብቁ፣ ከስራ ውጪ ባለው አኗኗራቸውም በማህበራዊ ሕይወታቸው የሚደሰቱና የሆነ ነገር ለሕብረተሰቡ የሚያበረክቱ መሆን አለባቸው ባይ ናቸው ዶ/ር አረጋ፡፡ በአጠቃላይ በቡድን ስራ የሚያምኑ፣ ሌላውንም ለማገልገል የቆረጡ፣ በጥቅም ብቻ ያልታወሩትን ሠራተኞቼን እወዳለሁ ይላሉ።

አቶ እታለማሁ በየትኛውም መልኩ የሠራተኞችን ሁለንተናዊ ይዘት የጠበቀ ሥራ እንዲተገበርና በዚህ መልኩም አይደለም ታች ያለው ሠራተኛ አመራሩም ከአምባገነንነት ርቆ በስራው ብቻ የሚያምን እንዲሆን ዘመናዊ የመሪነት ሚናን ያለማመዱ ታላቅ ሰው ናቸው የሚላቸውም ለዚህ እንደሆነ ይናገራል፡፡ እኔ ብቻ ያልኩት ይሁን የማይሉና የሌሎችንም ሃሳብ ለማዳመጥ ዘወትር ዘግጁ ስለሆኑ ሁላችንም ያለፍርሃትና መሸማቀቅ ስራችንን ዋስትና አድርገን አንድንሰራ አድርገውናል ብሏል፡፡ ጥሩ ስራ የሚሰራው ሰውዬውን ስታለማው ነው የሚለው አመለካከታቸውም ውጤታማ አድርጎናል ይላል፡፡

የሚከተሉት የአመራር ጥበብ እኔ የምከተለው የአመራር ሲስተም ቀለል ያለ ነው ይላሉ ዶ/ር አረጋ። አለቃ ማለት እረኛ ነው፡፡ ከብቶቹ ከሌሉ እረኛው እንደማይኖረው ሁሉ የሠራተኞቹ መኖር ነው አለቃውን እንዲኖር ያደረገው፡፡ ስራችን የቡድን ስራ ነው፡፡ የስራ ክፍፍል እንጂ አለቃና ምንዝር የሚባል ነገር የለም፡፡ እኔ አንድ ስራ አለኝ፣ ፅዳት እህት ካለችኝም እሷም ስራ ነው የምትሰራው፡፡ ሌላውም እንደዚያው፡፡ የሁላችንም የጋራ ተግባር የኩባንያውን ህልውና በጋራ ያረጋግጣል ይላሉ ዶ/ር አረጋ፡፡ አለቅነት ማለት ስራን በአግባቡ መምራት ማለት ነው፡፡ ልክ እረኛው ላሞቹን ወደ ገደል እንዳይገቡ፤ የሰው ማሳ እንዳያጠፉ እንደሚጠብቀው ሁሉ አለቃም የሠራተኛውን ስብዕና እየጠበቀ፣ ለለውጥና ለዕድገት እያዘጋጀ፣ እንዲተካው መንገድ እየጠረገ አብሮ የሚጓዝ ከሆነ እልቅናውን በአግባቡ ተወጥቷል ማለት ነው ይላሉ፡፡ አለቃ ሲወጣም ሆነ ሲገባ እየተደበቀ ከሆነና ሠራተኞቹ እንዳያዩት ራሱን ልዩ በሆነ መስታወት ውስጥ የሚጋርድ ከሆነ አበቃለት ይላሉ፡፡ አለቃ ሠራተኞች የፈለጉትን እንዲጠይቁ መፍቀድ አለበት። የአለቃው ኃላፊነት መልስ መስጠት ነው፡፡ መልስ መስጠት ማለት ደግሞ ሠራተኛው ይሄን ያህል ብር ስጠኝ ቢልህና ካልቻልክ ለምን እንዳልቻልክ በአግባቡ ማስረዳት ማለት ነው ባይ ናቸው፡፡

ስለ መሠረታዊ ማህበርዶ/ር አረጋ ሠራተኞቻቸው የሠራተኛ ማህበር እንዲያቋቁሙ ከሚገፋፉት ሠዎች መካከል ዋናው መሆናቸውን ይናገራሉ። እናቋቁም ብለው ሳይጠይቁን ማህበር አቋቁሙ ያልኳቸው ያለምክንያት አይደለም ይላሉ። የሠራተኛ ማህበር ካለ ብዙ ሥራህን ያቃልልልሀል፡፡ 500 ሠራተኛ ያለበት ቦታ ሄደህ ከምትቸገር 10 ሰዎች ከመካከላቸው ተመርጠው ከሆነ ከእነሱ ጋር መወያየትና መስማማት ስራህን ያቀላጥፍልሀል፡፡

ችግር ሲፈጠርብንም የሕብረት ስምምነቱን የፃፍነው እኛው ስለሆንን በዚያ መሠረት እንፈታዋለን፡፡ በእርግጥ ኩባንያዎቹና ተግባራቸው የተለያየ ስለሆነ አንዱ ኩባንያ ላይ የምታገኘው አበል ከሌላው ሊለይ ይችላል፡፡ ሌሎቹ ጥቅሞች በሙሉ ግን አንድ ዓይነት ናቸው፡፡ የሰው ኃይል ፖሊሲ ማኑዋል አለን፡፡ በዚህም በሰው ኃይሉና በአመራሩ በኩል ያለው ልዩነት እየጠበበ መጥቷል፡፡ አንድ ቀን አንድ ይሆናል ብለን እናምናለን ይላሉ ዶ/ር አረጋ፡፡

በእርግጥ የሠራተኛ ማህበር ስለማቋቋም የተያዘው ባህልና ታሪካዊ አመጣጡ የተጨቆኑ ሠራተኞች የጀመሩት ተደርጎ ስለሚወራ እንጂ የእኛ ኩባንያዎች ማህበር ያቋቋሙት በእኛ ግፊት ነው፡፡ አሠሪ ጨቋኝ ሠራተኛ ተጨቋኝ ነው የሚለው ፍልስፍና ተይዞ ሁለቱን የማስታረቅ ነገር ነው የተለመደው የሚሉት ዶ/ር አረጋ በእኔ እምነት አንድ ቀን አሠሪና ሠራተኛ የሚለው ነገር ይጠፋል። መጥፋትም አለበት እላለሁ ምክንያቱም የሥራ ክፍፍል እንጂ ሁላችንም ሠራተኞች ነንና ብለዋል። ሁላችንም የድርጅቱ ቅመሞች ነን፡፡ ከእኔ ጀምሮ ያለነው ሁላችንም ሠራተኞች ነን፡፡

የወደፊት ህልማቸው ላለፉት ዓመታት የለፋንባቸው የአሠራር ስርዓቶች ይጠቅማሉ ብዬ ስለማምንና እንዲቀጥል ስለምሻ ብዙ ወጣቶችን ለቀጣይ ትምህርት በማዘጋጀት በሁለተኛ ዲግሪ እንዲሰለጥኑ እያደረኩ ነው ይላሉ። ይህን ባህል እያጠናከርን ስንሄድ ከመካከላቸው መሪ የሚሆኑ ወጣቶች እየፈለቁ በአንድ ሰው ከመሽከርከር ፈንታ በቡድን ስራ የሚያምኑ እየበዙ አገሪቱንም ሆነ የእኛንም ካምፓኒዎች ይጠቅማሉ የሚል እምነት አለኝ ብለዋል፡፡

ሌሎች በግሩፕ ያልተደራጁ የሼህ መሐመድ ድርጅቶችም በየቦታው ይኖራሉ፡፡ እነዚህም ወደ ግሩፑ መቀላቀላቸው ከዚህኛው ልምዱን ያገኙታል ብዬ አስባለሁ፡፡ ከዚህ ሌላ የሚድሮክ አካሄድና ያለው ስም ግዙፍ ስለሆነ እኛም በስሩ ያለን ሰዎች መጠንከር አለብን፡፡ ሚድሮክ በሚለው ሼክ መሐመድ በሚለው ታላቅ ደረጃ መጠራት ከፈለግን ተግባራችን ሁሉ ከኢንዱስትሪዎቹ ጋ እኩል በመቃኘትና በመንቀሳቀስ ማሸነፍ ይገባናል ብዬ አስባለሁ፡፡ አሁን ውድድሩ በአገሪቱ እየሰፋ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሌሎች አዳዲስ ኢንቨስተሮችና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች እየበዙ መጥተዋልና ብለዋል፡፡ እንደ ሼህ መሐመድ ዓይነት ኢንቨስትመንትን ከመጀመርና ሌሎችን ከመሳብ አኳያ ያላቸው ሚና ቀላል አይደለም ብዬ አስባለሁ፡፡ ምክንያቱም ከማሳየት ረገድና የሚሰጠውን አገልግሎት እያዩ ሌሎች እንዲመለከቱ ለማድረግ የተከፈለው መስዋዕትነት ቀላል አይደለምና፡፡

ሌሎች ባለሃብቶችም ሳይሳቀቁ እነማን አሉ? ለስንት ዓመት ቆዩ? ምን ጥቅም አገኙ? የሚለው ጉዳይ ለእኛ ቀላል ስላልሆነ ሚድሮክ የነበረበትን ጥንካሬ ይዞ እንዲቀጥል መጠንከር አለብን። እኛ የሚጎዳ ተግባር ብንፈጽም፣ ከመንግሥት ጋር የሚጣረስ ቋንቋ ቢኖረን አገሪቱን ይጎዳል፡፡ ለዚህ ደግሞ የሚተኩንን ሰዎች በስፋት ማሰልጠን አለብን። ባለሃብቱም ሆኑ እኛ ሠራተኞቻቸው እናልፋለን። ግን ከአሁኑ የሚተኩንን ሰዎች የስራና የሰው ፍቅር አንዲኖራቸው ለማድረግ መሠረት ጥለናል ብዬ አስባለሁ፡፡

General KnowledgeMemorable Quotes About Customers

”People don’t want to communicate with an organization or a computer. They want to talk to a real, live, responsive, responsible person who will listen and help them get satisfaction.”

- Theo Michelson, State Farm Insurance

"Your most unhappy customers are your greatest source of learning." Bill Gates, Microsoft

"It's customers that made Dell great in the first place, and if we're smart enough and quick enough to listen to customer needs, we'll succeed." Michael Dell, Dell

"If you work just for money, you'll never make it, but if you love what you're doing and you always put the customer first, success will be yours." Ray Kroc, McDonalds

Well done is better than well said.”- Benjamin Franklin

”The true leaders serves. Serves people. Serves their best interests, and in doing so will not always be popular, may not always impress. But because true leaders are motivated by loving concern than a desire for personal glory, they are willing to pay the price.”

- Eugene B. Habecker

Page 12: ከሊቀመንበሩ ማኅደር University Conducted 11th Annual

12

MIDROC NewsletterVolume 13, Issue # 67 April — June 2012

Addis Ababa, Ethiopia

Ethiopia has been implanting radical policy and structural changes with a view to transforming the country through the realization of robust and far-reaching development objectives in economic and social sectors. As a result, remarkable and exemplary progressive growth has been registered in the last few years in physical and social infrastructures, business and education, trade and investment, information and communication technology, etc.

MIDROC, being the pioneer business community in Ethiopia, has been making huge Foreign Direct investment in diverse economic activities, thus playing key role in making a difference in the overall development endeavors of the country.

The World Economic Forum is an independent international organization that plays an indispensible role in creating a better world for all humanity. Its founding principles and major developmental issues are shared by

More than 700 participants from over 70 countries had attended the World Economic Forum on Africa from May 9 – 12, 2012 to address the continent’s transformation and seek solutions to challenges facing the region.

The Forum was held at the African Union Conference hall in Addis Ababa, Ethiopia.

This column carries welcome message delivered by CEO, MIDROC Ethiopia, Dr. Arega Yirdaw through ”Destination Ethiopia” magazine which was published and distributed at the forum.

most of the African governments, business communities, and people who are showing real commitment more than ever before to attain sustainable growth and development in their respective countries.

The convention of the World Economic Forum in Addis Ababa, which is expected to bring together world and African leaders, business and social entrepreneurs, and other renowned personalities in key contemporary issues of our world, will definitely have a long-lasting positive effect in Africa and Ethiopia in sustaining the development endeavors being undertaken by all stakeholders.

MIDROC extends its profound appreciation to the Forum for choosing Ethiopia to host its 2012 meeting on the theme of Transforming Africa here in Addis Ababa, the diplomatic hub of Africa.

MIDROC welcomes the participants of the World Economic Forum and wishes all a pleasant and fruitful stay in Addis Ababa.

Message from CEO

ዶ/ር አረጋ ይርዳውDr. Arega Yirdaw

ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ኦፊሰር፣ ሚድሮክ ኢትዮጵያChief Executive Officer, MIDROC Ethiopia

u’í ¾T>�ÅM (Distributed at no Cost)

Address: Office of the Chief Executive Officer, MIDROC EthiopiaFax: +251-11-371-5988 / 372-4977P.O. Box: 5787, Addis Ababa EthiopiaE-mail: [email protected]: www.midroc-ethiotechgroup.com

mL:KT½ kcEF x@Gz!k!†tEV åðsR